VOA Amharic

VOA Amharic

12.6K subscribers

Verified Channel
VOA Amharic
VOA Amharic
February 26, 2025 at 04:38 PM
ደቡብ አፍሪካ 127 የሚኾኑ ወታደሮቿን ከኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ አስወጥታለች፡፡ አራቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው መኾኑም ታውቋል። ወታደሮቹ ከሁለት ዓመታት በፊት የ16 ሀገራት ጥምር በሆነው በደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማኅበረሰብ ወይም ሳድክ ኅይል ውስጥ ታቅፈው፣ በሩዋንዳ ከሚደገፈው ኤም 23 ጋራ በመፋለም ላይ ያለውን የኮንጎ መንግሥት ለመደገፍ የተሠማሩ ነበሩ። https://amharic.voanews.com/a/s-africa-repatriates-more-than-120-soldiers-from-dr-congo/7988946.html ሃያ አንዱ ወታደሮች ትላንት ማክሰኞ የተመለሱ ሲሆን፣ 106 የሚሆኑት ደግሞ ዛሬ ረቡዕ ተመልሰው ደቡብ አፍሪካ ወታደሮቿን በሙሉ አስወጥታ አጠናቃለች፡፡ የተጎዱት ወታደሮች ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ፣ ከተመለሱት ውስጥ አንዳንዶቹ የሥነ ልቦና ሕክምና እንደሚያስፈልጋቸውም ታውቋል።
👍 ❤️ 🥺 8

Comments