VOA Amharic

VOA Amharic

12.6K subscribers

Verified Channel
VOA Amharic
VOA Amharic
February 26, 2025 at 05:10 PM
የኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ ነገ ሐሙስ በሶማሊያ ጉብኝት በማድረግ ከሀገሪቱ ፕሬዝደንት ሃሳን ሼክ ሞሃሙድ ጋራ እንደሚወያዩ ከሶማሊያ ከመንግሥት ምንጮች መረጃውን ማግኘቱን ኤኤፍፒ አመልክቷል። https://amharic.voanews.com/a/abiy-ahmed-somalia/7988983.html ሁለቱ ሀገራት የሻከረውን ግንኙነታቸውን ለማደስ በመሞከር ላይ ባሉበት ወቅት የሚካሄደው ጉብኝት “በአንካራ የተፈጸመውን ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግና ለማጠናቀቅ ከሚደረጉ ሰፊ ጥረቶች አንዱ እንደሆነ” ዘገባው አመልክቷል። “በጠቅላይ ምኒስትር ዐብይ አህመድ የሚመራ ከፍተኛ የባለሥልጣኖች ቡድን ነገ ሞቃዲሹ እንደሚደርስ ይጠበቃል” ሲሉ ለፕሬዝደንታዊ ቤተ መንግሥቱ ቅርብ የሆኑና ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ምንጭ መናገራቸውን ኤኤፍፒ በዘገባው አመልቷልክ።
❤️ 👍 😂 😮 🥺 6

Comments