VOA Amharic
February 26, 2025 at 06:42 PM
የአእዋፍ እንፍልዌንዛ ባለፉት ሦስት ዓመታት በአሜሪካ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዶሮዎችን በመግደሉና ከፍተኛ የእንቁላል እጥረት በመከሰቱ መንግሥት በሽታውን ለመዋጋትና ከውጪ እንቁላል ለማስገባት 1 ቢሊዮን ዶላር መመደቡን የሀገሪቱ የግብርና ምኒስትር አስታውቀዋል።
https://amharic.voanews.com/a/us-bird-flu/7989104.html
ባለፉት ሦስት ዓመታት በተከሰተው የአእዋፍ እንፍሉዌንዛ 166 ሚሊዮን ዶሮዎች መሞታቸውን የአሜሪካው የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሽታው አንድ ሺሕ የሚሆኑ የወተት ላሞችንና 70 የሚሆኑ ሰዎችንም ማጥቃቱ ታውቋል። ባለፈው ዓመት አንድ ሰው በበሽታው ሞቷል።
❤️
👍
😂
3