Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
February 7, 2025 at 09:43 AM
የ4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑ ተገለፀ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በተገኙበት የቅድመ ዝግጅት ሥራው ያለበት ደረጃ ተገምግሟል፡፡ የውድድር ፓኬጁን ጨምሮ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎቹ እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ ክብር ዶ/ር ተሻለ ገልፀዋል፡፡ በሁሉም ክልሎች ከተቋማት ጀምሮ በየደረጃው በሚካሄድ ውድድር አሸናፊ የሆኑ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና ኢንተርፕራይዞች የሚካፈሉበት ትልቅ ሀገራዊ ሁነት እንደሆነም ተመላክቷል፡፡ ውድድሩ ክህሎት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ከማፋጠን አኳያ ያለውን ሚና በሚያልቅ መልኩ እንደሚካሄድም ነው የተገለፀው፡፡ 4ኛ ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የዓለም አቀፉ የክህሎት ተቋም ኢትዮጵያን አባል ሀገር አድርጎ ከተቀበለ በኋላ የሚካሄድ የመጀመሪያው ውድድር ነው፡፡ ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ ጥር 30፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/
👍 1

Comments