Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia WhatsApp Channel

Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia

4.8K subscribers

About Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia

Welcome to the official whatsApp channel of the Ministry of Labor & Skills - Ethiopia. The channel is used to provide information and updates related to skills development, job creation, and other labor-related matters in the country.

Similar Channels

Swipe to see more

Posts

Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
6/11/2025, 9:41:35 AM

ለውጭ ሀገር የሥራ ፈቃድ አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ዜጎች አዲስ የሥራ ፈቃድ ፣ የእድሳት፣ የክሊራንስና የጠፋና የተበላሸ ሥራ ፈቃድ ምትክ አገልግሎት በሥራ ገበያ መረጃ ድረገፅ www.lmis.gov.et አማካኝነት በቀጥታ እየሰጠ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ አሁን ደግሞ ተጠቃሚዎች የአገልግሎት ክፍያቸውን በቴሌብር አማካኝነት መፈፀም፣ የሚላክላቸውን IMV ቁጥር ተጠቅመው የሥራ ፈቃዳቸውን በድረ ገፁ ላይ ማግኘትና ወደ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መ/ቤት መምጣት ሳይጠበቅባቸው አትመው መጠቀም የሚችሉ መሆኑን እናስታውቃለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ አገልግሎቱን በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በኩል ማግኘት እንደሚችሉም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ሥራና ክህሎት ሚኒስቴር For All Foreign Work Permit Applicants The Ministry of Labor and Skills now provides all foreign work permit services—including new applications, renewals, clearances, and replacements—online via www.lmis.gov.et. Applicants can pay service fees through Telebirr, use the provided IMV number, and print their permits directly from the website—eliminating the need to visit the Ministry in person. Services are also available at the Mesob One-Stop Service Center. Ministry of Labor and Skills

Post image
💞 2
Image
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
6/7/2025, 5:36:13 AM

የደቡብ ኢትዮጵያ ለኮሌጅ አመራሮችና አሰልጣኝ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ጀመረ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ለኮሌጅ አመራሮችና አሰልጣኝ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ምዘና መስጠት ጀምሯለሰ። የቢሮ ኃላፊ እቶ አብዮት ደምሴ በአርባ ምንጭ ክላስተር የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ማስጀመሪያ መድረክ ላይ ምዘናው በክልሉ በሰባቱ ክላስተሮች የሚከናወን ሆኖ በአርባ ምንጭና በቦዲቲ ክላስተር ምዘና ሂደቱ መጀመሩን አሳውቀዋል። የብቃት ማረጋገጫ  ዓላማ በራሱ የሚተማመን ብቃት ያለው ዜጋ መፍጠር ፣  የክህሎትና የዕውቀት ክፍተትን በመለየት ማሟያ ግብዓት ዝግጅት በማድረግ ብቁና ተወዳዳሪ አሰልጣኝ ማፍራት መሆኑ ተገልጿል፡፡ የአሰልጣኝ መምህራን የክህሎት ክፍተት ማሟያ ስልጠና በ2016 ዓ/ም ክረምት መሰጠቱን ጠቅሰው በ2017 ዓ/ም ክረምትም የክህሎትና የዕውቀት ክፍተት በምዘና ከተለየ በኋላ ክፍተቱን መሰረት በማድረግ ምዘናው የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ግንቦት 30፤ 2017 ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ይከታተሉን፡ በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com

👍 2
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
6/5/2025, 7:32:51 PM
Post image
👍 ❤️ 9
Image
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
5/30/2025, 9:43:16 AM

የደብረብርሃን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001 የጥራት የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርቲፊኬት አገኘ ኮሌጁ ከኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የISO 9001 የጥራት የሥራ አመራር ሥርዓት ሰርቲፊኬቱን ተረክቧል። የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ኮሌጁ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት የዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላቱን በተከናወነለት የኦዲት ሂደት ተገምግሞ ብቁ ሆኖ በመገኘቱ ሰርቲፊኬቱን እንዳገኘ አመላክቷል። በርክክብ ስነ ስርዓቱ የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ክብርት ኢ/ር መዓዛ አበራ የእንኳን ደስአላችሁ መልእክት አስተላልፈው መንግስት ለጥራት ልዩ ትክረት በመስጠት ዘመናዊ የጥራት መንደር በመገንባትና አስፈላጊ የጥራት መገልገያ መሳርያዎችን በማሟላት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት እየሰጠ  መሆኑን ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ግንቦት 22፤ 2017 ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ይከታተሉን፡ በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com

Post image
Image
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
5/27/2025, 4:14:59 AM

የወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ትሩፋት ስራ ከቁጥር ባለፈ ትርጉም ባለው መንገድ የዜጎችን ህይወት ሊቀይር እንደሚገባ ተገለፀ። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ75 ቀናት የስራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ትሩፉትና የንቅናቄ ስራዎች አፈፃፀም እንዲሁም ከስኬት ባንክ ጋር በመቀናጀት በባንኩ ዲስትሪክቶችና ቅርንጫፎች የተደረገ ኦዲት ሪፓርት በመገምገም ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። በግምገማ መድረኩ በዘጠና ቀናት የንቅናቄ ዕቅዱ በ35ኛው ቀን የግምገማ መድረክ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈፃፀምን ጨምሮ በ75 ቀናቱ በስራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ትሩፉት ስራዎች የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት አፈፃፀም ቀርቧል። ባለፉት 75 ቀናት በስራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ትሩፉት ንቅናቄ ስራ በተከናወኑ ተግባራት በበጀት ዓመቱ ለመፍጠር ከታቀደው 300ሺ የስራ ዕድል ፈጠራ በ10 ወራት ከ15 ቀናት ውስጥ ብቻ 324ሺ282 ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉ የተገለፀ ሲሆን በዚህም ከዕቅድ በላይ መፈፀም መቻሉ ተገልጿል። ነባርና አዲስ ኢንተርፕራይዞችን በኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርአት E-LMIS ከመመዝገብ አንፃር 13ሺ15 ኢንተርፕራይዞች ማደራጀት መቻሉንና አሁንም ከውጤታማነት አንፃር ክፍተት መኖሩ ተገልጿል። በሌማት ትሩፋት 2ኛ ዙር ንቅናቄ መርሀ ግብር አምስት ግቦች ተጥለው ወደ ተግባር መገባቱ የተገለፀ ሲሆን በዘርፉ ለ9ሺ528 ዜጎች የስራ ዕድል መፍጠሩ ተመላክቷል። በንቅናቄ በተሰራው ስራ የግብአት አቅርቦት ችግር ለመፍታት ጥረት መደረጉንና የከተማ ግብርና ስራ ባህል እየሆነ መጥቷል ተብሏል ነገር ግን ወቅታዊ የኑሮ ውድነትና የገበያ ዋጋ ከማረጋጋት አንፃር አሁንም በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል። የግምገማ መድረኩ ሌላኛው የትኩረት ነጥብ ከብድር አቅርቦት ጋር በተያያዘ ስኬት ባንክ እያደረገ ያለው የፋይናንስ አቅርቦት እንዲሁም ብድር ለመስጠት የባንኩ ቅድመ ሁኔታዎች ምን ይመስላሉ የሚለውን በመዳሰስ ከብድር ፈላጊዎች ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ አሟልቶ አለመቅረብ አንዱ ተግዳሮት መሆኑ ተገልጿል። የውይይት መድረኩን የመሩት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራና የሌማት ትሩፋት ስራ ከቁጥር ባለፈ ትርጉም ባለው መንገድ የዜጎችን ህይወት ሊቀይር ይገባል ብለዋል። አቶ ጥራቱ አያይዘውም በየጊዜው በተካሄዱ የግምገማ መድረኮች በክፍለ ከተሞች መካከል የፉክክር መንፈስ በመፍጠር በአፈፃፀም ዝቅተኛ የነበሩ ጽሕፈት ቤቶች ደረጃቸውን እንዲያሻሽሉ አስችሏል ሲሉ ተናግረዋል። የሌማት ትሩፋት ስራውን ከሌሎች ተግባራት ጋር አቀናጅቶ በምራት የኑሮ ውድነቱን በማረጋጋት ያለውን አስተዋፅኦ በመረዳት በትኩረት መሰራት እንዳለበትም በመድረኩ ተጠቁሟል። የግምገማ መድረኮቹ ዓላማ የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ መሆኑን በመረዳት በቀሪ የበጀት ዓመቱ ጊዜያት ዕቅዱን ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አቅጣጫ መቀመጡን ከቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ግንቦት 19፤ 2017 ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ይከታተሉን፡ በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com

Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
2/7/2025, 9:43:03 AM

የ4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተጠናቀቁ መሆኑ ተገለፀ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በተገኙበት የቅድመ ዝግጅት ሥራው ያለበት ደረጃ ተገምግሟል፡፡ የውድድር ፓኬጁን ጨምሮ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎቹ እየተጠናቀቁ እንደሚገኝ ክብር ዶ/ር ተሻለ ገልፀዋል፡፡ በሁሉም ክልሎች ከተቋማት ጀምሮ በየደረጃው በሚካሄድ ውድድር አሸናፊ የሆኑ ሰልጣኞች፣ አሰልጣኞችና ኢንተርፕራይዞች የሚካፈሉበት ትልቅ ሀገራዊ ሁነት እንደሆነም ተመላክቷል፡፡ ውድድሩ ክህሎት ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማትን ከማፋጠን አኳያ ያለውን ሚና በሚያልቅ መልኩ እንደሚካሄድም ነው የተገለፀው፡፡ 4ኛ ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የዓለም አቀፉ የክህሎት ተቋም ኢትዮጵያን አባል ሀገር አድርጎ ከተቀበለ በኋላ የሚካሄድ የመጀመሪያው ውድድር ነው፡፡ ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ ጥር 30፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/

👍 1
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
2/3/2025, 3:55:22 PM
Post image
Image
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
2/8/2025, 8:10:26 AM
Post image
Image
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
2/3/2025, 3:55:27 PM

ሪፎርሙ ለውጡን በሚመጥንና ለዜጎች ጊዜውን የዋጀ አገልግሎት መስጠት በሚያስችል መልኩ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም የመጀመሪያ ምዕራፍ አፈጻጸምን ገምግሞ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ በመድረኩ በመጀመሪያ ምዕራፍ የተከናወኑ ተግባራት በዝርዝር ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ ለትግበራው የሚያስፈልጉ የሰነድና የህግ ማዕቀፎች እንዲሁም አደረጃጀትን ጨምሮ አስፈላጊ የሆኑ ሥራዎች እንደተጠናቀቁ ተጠቁሟል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፤ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያው ተቋማዊ ልህቀትን በሚያረጋግጥ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ ርብርብ ሲደረግ ቆይቷል፡፡ በዚህም የመጀመሪያውን ምዕራፍ በማጠናቀቅ የቀጣዩን ምዕራፍ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መደላድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ በቀጣይ ሪፎርሙ ለውጡን በሚመጥንና ለዜጎች ጊዜውን የዋጀ አገልግሎት መስጠት በሚያስችል መልኩ ተግባራዊ እንደሚደረግም አመላክተዋል፡፡ የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍናን፣ ተደራሽነትንና ፍትሃዊነትን ለማሳደግ እንዲሁም ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ቴክኖሎጂ በሰፊው ጥቅም ላይ እንደሚውልም ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና በተጠሪ ተቋማቱ ላይ በሚተገበረው የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም ላይ ግልጽነት ለመፍጠር የሚያስችል ውይይት በየደረጃው ሲካሂድ ቆይቷል፡፡ ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ ጥር 26፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/

👍 1
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
2/8/2025, 8:10:28 AM

#አሁን #HappeningNow ‘ሥነ-ምግባራዊ አመራርነት ለተቋማዊ ተልዕኮ ስኬት’ በሚል መሪ ሀሳብ ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን መከላከያ ስልቶች ላይ ያተኮረ የውይይት እና የስልጠና መድረክ እየተካሄደ ይገኛል። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የፌዴራል የጸረ ሙስና ኮሚሽን በጋራ ያዘጋጁት የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን መከላከያ ስልቶች ላይ ያተኮረ ስልጠና ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ተሻለ በሬቻ(ዶ/ር) ጨምሮ የሚንስቴር መስሪያ ቤቱ እና የተጠሪ ተቋማት እንዲሁም የፌዴራል የጸረ ሙስና ኮሚሽን የሥራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ ነው። ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡ የካቲት 1፤ 2017 በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/

❤️ 1
Link copied to clipboard!