
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
February 13, 2025 at 07:25 PM
💡ስልጠና የስኬት መግቢያ በር💡
📌 በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት የመጠቀም ሀሳብ ካለዎት የመጀመሪያው ጉዳይ በኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (www. lmis.gov.et )ላይ መመዝብ ነው፡፡
📌 ሁለተኛውና ሊታለፍ የማይችለው ነገር ስልጠና ነው፡፡ ልብ ይበሉ! ለውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስልጠና ወሳኝ ብቻ ሳይሆን የስኬት መግቢያ በር ነው፡፡
📢ስልጠና ለምን?
✅ ብቃትና ተወዳዳሪነትዎን ይጨምራል፣
✅ መብትና ግዴታዎን አውቀውና የሥነ-ልቦናም ጨምር ዝግጅት እንዲያደርጉ ያግዝዎታል፣
✅ የሚሄዱበትን ሀገር ባህልና ቋንቋ እንዲያውቁና ከአሠሪዎ ጋር የተሻለ ግንኙነት መፍጠር ያስችልዎታል፣
✅ ሁለንተናዊ ደህንነትዎ እንዲጠበቅ ፋይዳው የላቀ ነው፣
✅ የወደፊትህ ህልምዎን ለማሳካት ተጨማሪ አቅም ይፈጥርልዎታል፡- በመስኩ ለ21 ቀናት የሚሰጠው ስልጠና ከሙያዊው ክህሎት ባለፈ ስለገንዘብዎ አስተዳደርና የራስ ሥራ ፈጠራ ላይ እውቀት እንዲኖርዎ የሚያደርጉና መሰል የህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን ያገኛሉ፡፡
🚨ልብ ይበሉ!🚨
✅ ስልጠናውን ካጠናቀቁ በኋላ የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ይወስዳሉ፡፡
✅ የምዘናው ዋና ዓላማ ሰልጣኞችን ለማሳለፍና ለመጣል ሳይሆን በሚሰራው ሥራ ላይ ያሉ ክፍተቶችን አይቶ ለመሙላት ነው፡፡
✅ ይህም ብቃትዎንና ተወዳዳሪነትዎን የሚያሳድግ ነውና በፍጹም ህገወጥ የብቃት ማረጋገጫ ለመግዛት እንዳይሞክሩ!
💡 ስልጠና = ብቃት = ስኬት 💡
✅ ስልጠና ይውሰዱ! ብቃትዎን በምዘና ያረጋግጡ! ክፍተት ካለብዎ ክፍተትዎን ሞልተው ህልምዎን እውን ያድርጉ! ይህን መረጃ ለወዳጅ ጓደኛዎ በማጋራት #ከመሄድዎበፊትይሰልጥኑ ይበሏቸው፡፡
✅ ህጋዊ አማራጭና ደህንቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን እውን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት ይቀላቀሉ!
✅ ራስዎን ለአደጋ ከሚያጋልጥ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ይጠብቁ!
#ከመሄድዎበፊትይሰልጥኑ #ደህንነቱየተረጋገጠየውጭሀገርሥራስምሪት
#trainbeforeyougo #trainingmatters
#legaloverseasemployment #overseasopportunities
#ህጋዊአማራጭ #ደህንነቱየተጠበቀሥራስምሪት
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ ፡
የካቲት 6፤ 2017
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols
ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
ቲክቶክ:- tiktok.com/@mols_official
ሊንክዲን፡- https://www.linkedin.com/.../ministry-of-labor-skill-fdre/

❤️
1