
ዮናስ ቲዩብ - yonas tube
February 22, 2025 at 06:11 AM
❗❗#ቅበላ_ምንድን_ነው ?❗❗
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
🔴👉 ቅበላ ማለት በእንግድነት ለሚመጣው እንግዳ ለእንግዳው የሚመጥነውን ያህል ክብር ለመስጠት አዘጋጅቶና ተዘጋጅቶ መቀበል ነው::
🔵👉 ቅበላው መንፈሳዊ ከሆነ በመንፈሳዊ ሕይወት ጸድቶ መዘጋጀት ነው:: መጪው ጾም ከሆነ ለዚህ እንግዳ ንስሐ መግባትን በመጾም በመስገድ በጾሙ ወቅት ለሚፈጸሙ ሥርዓቶች ራስን አዘጋጅቶ መቀበል ነው:: በዚህም ምክንያት ቅበላን በመብል በመጠጥ ሳይሆን ጾምን ሯሷን ጹመው ቅበላ ያደርጉባታል አበው::
🔴👉 ምክንያቱም በጉጉት የሚጠብቋት የሚጠቀሙባት በዓመት የሚናፍቋትን የጾም እንግዳ ሊቀበሉ ነውና! እንግዳ ሲመጣ እንደ እንግዳው ክብር መዘጋጀት ይገባልና:: እኛ ልጆቻቸው ዛሬ እንደሚታየው እንደነርሱ ባንሆን እንኳ እነርሱ የሰሩትን ሥራ ሠርተን ልንመስላቸው ይገባናል እንጂ መጠጥ ቤቱን ጭፈራ ቤቱን የዝሙት መንደሩን ልናጨናንቅ አይገባም::
🔵👉 መፅሐፍ ከእንደዚህ ካለ ግብርም መንደርም ራቁ ተለዩ ነው የሚለው። ቅበላ ምግብን በመበቀል አልነበረም አይደለምም:: በጾም እንደ አበው ነው::
መንፈሳዊ ዝግጅትን በማድረግ ነገር ግን ለክርስቲያኖች በማይገባ በመብል በመጠጥ በዝሙት በጭፈራ በዳንኪራ ጾምን መቀበል ነውር ነው:: ኽረ ኃጢአትም ነው።
🔵👉 አንድ መንፈሳዊ ሰው ክርስቶስን ነው የተሸከመው በክርስቶስ ነውና ክርስትናን ያገኘው እና ክርስቲያን መሆን አለበት:: አንድ ክርስቲያን እኔ ክርስቲያን ነኝ እኔ በክርስቶስ ክርስቲያን ነኝ የሚለው በክርስትናው ሲመላለስ ነው። ክርስትና ደግሞ በፍቅር ሕግ ተገዝቶ በሥርዓት መኖር ነው። ሁሉ ተፈቅዶልናል ነገር ግን ሁሉ አይጠቅመንም እንደተባለ።
🔴👉 አብዝቶ መብላትና መጠጣትን በማንኛውም ቀን ቢሆን ለክርስቲያን በዚህ ግብር መታደም መታየትም ማሰብም አይገባም:: በክርስቶስ ደም የከበረን ሰውነት በዝሙት፣ በሥካር፣ በጭፈራ በእንደዚህ ያሉ ግብር ማቆሸሽ የአሕዛብ ሥራ ነው ለክርሲቲያን ግን ተገቢ አይደለም::
❗👉 ክርስቲያኖች ቅበላቸው በየደብሩና በየገዳሙም ሱባኤ በማሰብ ንስሐ በመግባት የበደልነውን በመካስ የቀማውን በመመለስ በፊት ከሚበላው ከሚጠጣው ቀንሶ በመጥን ብቻ ሳይሆን በዓይነትም ቀንሶ ለመጪው ጾም ይዘጋጃል::
❗ስለዚህም አብይ ፆምን የካቲት 17 በዕለተ ሰኞ ለመቀበል እስከ የካቲት 16 ዕለተ እሁድ ድረስ መዘጋጀት አለብን ማለት ነው።❗
❗ፆሙን የፍቅር የሠላም የበረከት ያድርግልን። ፆም ፀሎታችንን ሁሉ እርሱ እንደ ሀጥያታችን ብዛት ሳይሆን እንደ ምህረትና ቸርነቱ ይቀበልልን።❗
❗#መልካም_ፆም❗
።።።።#ወስበሐት_ለእግዚአብሔር ።።።።
።።።።። #ወለወላዲቱ_ድንግል ።።።።።
።።።።። #ወለመስቀሉ_ክቡር ።።።።።
ዲ/ን ዮናስ ዘ ሆለታ ደብረ ኤዶም
የካቲት 15 /2017 ዓ.ም
ሆለታ
ፔጁን #like_follow_share በማድረግ ትክክለኛ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት እንዲሁም መረጃ ያግኙ
🔴👉 በቴሌግራም | Telegram
👇👇👇👇👇👇
https://t.me/joinchat_yonas_holet_debreedom
🔴👉 በዋትስአፕ | whatsapp
👇👇👇👇👇
https://whatsapp.com/channel/0029Va4Ter67T8bV5NlRGJ2w
🔴👉 በዩትዩብ | YouTube
👇👇👇👇👇👇
https://www.youtube.com/@yonastube
🙏
1