Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
June 7, 2025 at 05:36 AM
የደቡብ ኢትዮጵያ ለኮሌጅ አመራሮችና አሰልጣኝ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ጀመረ። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ለኮሌጅ አመራሮችና አሰልጣኝ መምህራን የብቃት ማረጋገጫ ምዘና መስጠት ጀምሯለሰ። የቢሮ ኃላፊ እቶ አብዮት ደምሴ በአርባ ምንጭ ክላስተር የብቃት ማረጋገጫ ምዘና ማስጀመሪያ መድረክ ላይ ምዘናው በክልሉ በሰባቱ ክላስተሮች የሚከናወን ሆኖ በአርባ ምንጭና በቦዲቲ ክላስተር ምዘና ሂደቱ መጀመሩን አሳውቀዋል። የብቃት ማረጋገጫ  ዓላማ በራሱ የሚተማመን ብቃት ያለው ዜጋ መፍጠር ፣  የክህሎትና የዕውቀት ክፍተትን በመለየት ማሟያ ግብዓት ዝግጅት በማድረግ ብቁና ተወዳዳሪ አሰልጣኝ ማፍራት መሆኑ ተገልጿል፡፡ የአሰልጣኝ መምህራን የክህሎት ክፍተት ማሟያ ስልጠና በ2016 ዓ/ም ክረምት መሰጠቱን ጠቅሰው በ2017 ዓ/ም ክረምትም የክህሎትና የዕውቀት ክፍተት በምዘና ከተለየ በኋላ ክፍተቱን መሰረት በማድረግ ምዘናው የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ግንቦት 30፤ 2017 ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ይከታተሉን፡ በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com
👍 2

Comments