Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia
June 17, 2025 at 12:00 PM
ተጠናክሮ የቀጠለው የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና የቴክኒክና ሙያ ተቋማት  የኮዲንግ ስልጠና በትኩረት እየሰጡ ይገኛል፡፡ በዚህም በርካታ ዜጎች አለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው ሰርተፍኬት ባለቤት መሆን ችለዋል፡፡ የኮዲንግ ስልጠናው በትኩረት እየተሰጠ ከሚገኝባቸው ክልሎች አንዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ይገኝበታል፡፡ በአሁን ወቅት 4 ሺህ የሚጠጉ ዜጎች በክልሉ በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የኮዲንግ ስልጠና እየወሰዱ ይገኛል፡፡ ከነዚህ መካከል በርካታዎች ስልጠናቸውን አጠናቀው የሰርተፍኬት ባለቤት መሆን ችለዋል፡፡ በክልሉ የኮዲንግ ስልጠና በትኩረት በመስጠት ጥሩ አፈጻጸም እያስመዘገቡ ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መካከል የወራቤ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ተጠቃሽ ነው፡፡ ኮሌጁ የኢትዮ ኮደርስ  ስልጠና አፈፃፁሙን በአሁን ወቅት 94 በመቶ ማድረሱን የኮሌጁ ዲን አቶ ቡላድ ናሙዝ ገልፀዋል፡፡ ኮሌጁ በቅድሚያ አሰልጣኝ መምህራን የኮዲንግ ስልጠናውን እንዲወስዱ በማድረግ  የሰርተፍኬት ባለቤት እንዲሆን ያደረገ ሲሆን 593 ሰልጣኞች  ስልጠናውን በማጠናቀቅ የሰርተፍኬት ባለቤት እንዲሆኑ አድርጓል፡፡ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ  ከታቀደው 740 የኢትዮኮደርስ  ሰልጣኞች እስከ ግንቦት 30/2017 ድረስ 696 ሰልጣኞች የሰርተፍኬት ባለቤት እንዲሆኑ በማድረግ የኮሌጁን የኢትዮ ኮደርስ አፈፃፀም 94% ማሳካት መቻሉን ከክልሉ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡ ሰኔ 10፤ 2017 ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ በሚከተሉት የማህበራዊ ትስስር ገፆች ይከታተሉን፡ በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE ቴሌግራም፦ https://t.me/fdre_mols ዋትስአፕ፡- https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y ቲክቶክ:- tiktok.com
Image from Ministry Of Labor & Skills - Ethiopia: ተጠናክሮ የቀጠለው የ5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና   የቴክኒክና ሙያ ተቋማት  የኮዲንግ ስልጠና በትኩረት እየሰጡ ...

Comments