Addis Ababa Education Bureau
Addis Ababa Education Bureau
June 2, 2025 at 07:23 AM
የሰኞ ማለዳ የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡ (ግንቦት 25/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀው የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር የተካሄደ ሲሆን በመድረኩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፣ የቢሮ ማኔጅመንት አባላትና ሰራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል። በመርሀ ግብሩ ላይ የቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሊ ከማል" አገልጋይ መሪነት " በሚል ርዕስ የአገልጋይ መሪ ምንነትና ባህሪያትን መሰረት ያደረገ ሰነድ አቅርበዋል :: በመድረኩ ላይ የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ትክክለኛ የአገልግሎት ስልቶችን በመረዳት እንደቢሮው ባህሪ የትምህርት ጉዳይን ጠንቅቆ በማወቅ ስራን የማስፈፀም አቅምን ማሳደግ እንዲሁም ባገኙት እውቀት መነሻነት ለመምራትና ለማገልገል ቁርጠኛ የሆነ ማንነት ከሁሉም አመራር ፣ ፈጻሚ ፣ ቡድን መሪና ዳይሬክተሮች የሚጠበቅ ተግባር መሆኑን ተናግረዋል :: የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ለማግኘት https://linktr.ee/aacaebc
Image from Addis Ababa Education Bureau: የሰኞ ማለዳ የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር ተካሄደ፡፡   (ግንቦት 25/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስ...

Comments