ShegerFM 102.1(ሸገር 102.1)
ShegerFM 102.1(ሸገር 102.1)
June 12, 2025 at 02:23 PM
ታሪክን የኋሊት ሰኔ 5 2017 በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፖብሊክ ፣ ራሱን አንግሶ፣ አጼ በጉልበቱ የነበረው ጄን ቤዴል ቦካሳ የይሙት በቃ ፍርድ የተፈረደበት በ1979 ዓ.ም በዛሬዋ እለት ነበር፡፡ ቦካሳ በቅኝ ገዥዋ ፈረንሳይ በወታደርነት ፣ በኢንዶ ቻይናና በአፍሪካ አገልግሏል፡፡ አገሩ ነፃ ከወጣች በኋላ በመከላከያ በሻለቃ አዛዥነት ተመድቦ ፣ በማዕረግም ወደ ኮሎኔልነት አደገ፡፡ ወደ ስልጣን እርከኑ የመጨረሻ ከፍታም፣ ጠጋ ጠጋ ያለው የሃገሪቱ የጦር ሀይሎች ኢታማዦር ከሆነ በኋላ ነበር፡፡ የጦር አዛዥነቱን ተጠቅሞ፣ ከግብረ አበሮቹ ጋር የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የነበረው ዴቪድ ዳከን በመፈንቅለ መንግስት አስወገደው፡፡ ዴሞክራሲ ሲመጣ፣ ፍትህ ሲነግስ፣ እና እኩልነት ሲደላደል፣ ስልጣኑን አስረክባለሁ ብሎ የመሪነቱን ስልጣን ጨበጠ፡፡ ብዙም ሳይቆይ ወደ ለየለት አምባገነንነት ጭልጥ ብሎ ገባ፡፡ ሕዝቡን በብረት መዳፍ ቀጥቅጦ እና አንቀጥቅጦ ገዛው፡፡ ሃገሪቱን እንደ ግል ንብረቱ ቆጥሮ የፈለገውን አደረገባት፡፡ ቃሉን ሕግ አድርጎ ሕዝቡን እያስረ፣ እየጨቆነ እየገደለ መከራውን አሳየው፡፡ ቦካሳ ፕሬዘዳንት መሆኑ ብቻ አላረካውም ፡፡ ስለዚህ የእድሜ ልክ ፕሬዘዳንት ነኝ ብሎ አወጀ፡፡ ይሄም አልበቃውም፡፡ ራሱን አፄ አሰኝቶ ዘውድ ጭኖ ንጉስ ሆኛለሁ አለ፡፡ በዓለ ሲመቱን ለማክበር ለ2 ቀናት ዝግጅት፣ ከ20 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ወጪ አደረገ፡፡ ይሄ ከዚያን ጊዜ የማዕከላዊ አፍሪካ የአመት በጀት ፣ ከሲሶ በላይ ነበር፡፡ ሕዝቡ ግን በከፍተኛ ድህነት ውስጥ ነበር፡፡ ሁሉም ነገር ማብቂያ አለውና፣ የቦካሳን አምባገነናዊ አገዛዝ ለማስወገድ በጉብኝት ሊቢያ ሳለ መፈንቅለ መንግስት ተካሄደ፡፡ ወታደሮች አሴሩ፡፡ መፈንቅለ መንግስቱን፣ ፈረንሳይም ትደግፈው ስለነበር ፣ ከትሪፖሊ ፣ ፓሪስ ሲደርስ ግዞተኛ አደረጉት፡፡ የስደት ጊዜውን በኮትዲቭዋር እንዲያደርግ ጠይቆ ስለተፈቀደለት ወደዚያው ሄደ፡፡ እጁ ተይዞ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ሞት ተፈረደበት ፡፡ ከሰባት አመታት እስራት በኋላ ወደ ማዕከላዊ አፍሪካ ተመለሰ፡፡ ከጥቂት አመታት እስር በኋላ ለእስረኞች ይቅርታ ሲደረግ ይቅርታ ተደርገለት፡፡ ከሶስት ዓመታት በኋላ በህመም ምክንያት አረፈ፡፡ ጄን ቤዴል ቦካሳ የሞት ፍርድ ከተፈረደበት 38 ዓመት ሆነ፡፡ እሸቴ አሰፋ https://youtu.be/7cgOGhmy5FY

Comments