
ShegerFM 102.1(ሸገር 102.1)
278 subscribers
About ShegerFM 102.1(ሸገር 102.1)
ሸገር 102.1 መስከረም 23፣2000 ዓ.ም ሥራ የጀመረ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የግል ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡ ጣቢያችን ለማንም ባለመወገን ለሁሉም በታማኝነትና በመልካም ሥነ ምግባር መልካም አገልግሎት በመስጠት የሚያምንና ለእነዚህም እሴቶች ትልቅ ክብር የሚሰጥ ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡ ሸገር የእናንተ ነው! https://bit.ly/33KMCqz
Similar Channels
Swipe to see more
Posts

የካቲት 14 2017 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚሰሩ ሴት ተመራማሪዎች ቁጥር ካለፈው ጊዜ የጨመረ ቢሆንም ከአጠቃላይ ቁጥሩ አንፃር ግን አሁንም በቂ አይደለም ተባለ፡፡ ከአራት ዓመት በፊት በተጠና ጥናት መሰረትም በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ሴቶች 16.9 በመቶ መሆኑን ያሳያል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አዳዲስ ሴት ተመራማሪዎችን ወደ መስመሩ ከማምጣት ባለፈም ያሉትም ቢሆን የሚገጥሟቸው ችግሮች ቀላል አለመሆናቸውን ጥናት አሳይቷል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ በዘርፉ የሴቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ጥናት ያሳያል የተባለ ሲሆን አሁን ያለው ቁጥር ግን በቂ አይደለም፤ ያሉትም ቢሆን ብዙ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ቆይቷል ተብሏል፡፡ ተቋማት ብቻ ሳይሆኑ የስራ ባልሰደረቦችም የተሳሳተ አመለካከት አለ፤ ጥናት እና ምርምር ስራዎች ቢኖሩም ጊዜ የላቸውም በሚል እንድንሳተፍ እድል አይሰጠንም ይላሉ፡፡ ሴቶቹ ባሉበት ዘርፍ ወደፊት እንዳይመጡ እንቅፋት ከሆነባቸው ችግሮች መካከል ሌላኛው ደግሞ በተቋሙ ያለው መዋቅር ውስብስብ መሆኑ ነው መባሉን ሰምተናል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ …. https://tinyurl.com/bd9tkh6d ፋሲካ ሙሉወርቅ የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q 📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd 📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s 📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il 📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r

የካቲት 14 2017 የአየር ንብረት ለውጥ የኢትዮጵያን ዓመታዊ ጥቅል ምርት ( #GDP ) በ10 በመቶ እየቀነሰው መሆኑ ተነግሯል፡፡ በዚህ ሳቢያ በሚደርስ የምርታማነት መቀነስ በአማካኝ በየዓመቱ 3 ሚሊዮን የሚደርሱ ኢትዮጵያውን ለምግብ እጥረት ይጋለጣሉ፤ በዚህም በተለይ ሴቶችና ህፃናት ይበልጥ ተጎጂ ናቸው ተብሏል፡፡ ይህ ተባለው ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ የተባለው ተቋም አጋር ካላቸው ተቋማት ጋር በመሆን የአየር ንብረት ለውጥ በስርዓተ ምግብና በስርዓተ ፆታ ላይ እያስከተለ ያለውን ጉዳት ለመከላከል የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ በሆነበት ወቅት ነው፡፡ በቢልና ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን የገንዘብ ድጋፍ ለ3 ዓመታት የሚቆየው ፕሮጀክት ይፋ በተደረገበት መርሃ ግብር ጥናታዊ ፅሁፍ ያቀረቡት በኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት ደህንነታቸው የተጠበቁና በምግብ ንጥረ ነገር የበለፀጉ ምግቦች ባለሙያ የሆኑት አቶ መሰረት ፀጋዬ፤ የአየር ጠባዩ መዛባት ተከታታይ የድርቅ አደጋዎችንም አስከትሏል፤ ለአብነትም ከ3 ዓመታት በፊት በዚህ ምክንያት በተከሰተው የድርቅ አደጋ በሰብልና በእንሰሳቱ ላይ የደረሰውን ውድመት እንኳን ብንመለከት ኢትዮጵያ በድርቁ ምክንያት 4.4 ቢሊዮን ዶላር ወይም በዚያን ወቅት በነበረው የምንዛሪ ስሌት 220 ቢሊዮን ብር እንዳጣች በዘርፉ የተደረገው ጥናት እንዳሳየ አቶ መሰረት ነግረውናል፡፡ ችግሩን የስርዓተ ምግብንና የስርዓተ ፆታን ጉዳይ ጋር በማስተሳሰር ለመስራት በማሰብ ፕሮጀክቱ እንደተጀመረ የነገሩን በፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ የፕሮጀክቱ የሞኒተሪንግና ኢቫሉዌሽን ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሰላም ኢሳያስ፤ ፕሮጀክቱ በ3 ዓመታት ጊዜ ቆይታው ከጉዳዩ ባለቤቶቨች ጋር ዙሪያ ውይይቶችን ያካሂዳል፣ጥናቶችንም ያደርጋል ብለውናል፡፡ በመንግስት የሚሰራው የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራ ሊበረታ ይገባል የሚሉት የስርዓተ ምግብ ባለሙያው አቶ መሰረት ፀጋ፤ በገጠር ያሉ ሴቶችን እንግልት ለመቀነስ ብሎም የደን መጨፍጨርን ለመከላከል የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ዝርጋታው በተለይም የሶላር ኤነርጂን በየገጠሩ ማዳረስ ይገባልም ብለዋል፡፡ የአየር ንብረት ለውጡ የ10 በመቶ እንዲቀንስ አድርጎታል የተባለው የኢትዮጵያ ጂዲፒ 100 ቢሊዮን ዶላር ወይም 12.5 ትሪሊዮን ብር መድረሱን የገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል፡፡ የገንዘብ ሚኒስቴር በቅርቡ ባወጣው የሩብ ዓመት አጠቃላይ የመንግሥት የዕዳ ሰነድ የውጭ ምንዛሪ ለውጡ ከመደረጉ አንድ ወር በፊት ማለትም በሰኔ 2016 ዓ.ም የአገሪቱ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት ሲሰላ 207 ቢሊዮን ዶላር የነበረ ሲሆን፣ የውጭ ምንዛሪ ለውጡ ከተደረገ በኋላ በ2017 ዓ.ም መስከረም ወር መጨረሻ ላይ ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር መውረዱን መናገሩ ይታወሳል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ …. https://tinyurl.com/352ftctf ምንታምር ፀጋው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q 📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd 📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s 📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il 📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r

የካቲት 14 2017 በኢትዮጵያ ቡናን እሴት ጨምሮ ከመላክ ይልቅ በጥሬው መላክ የተለመደ ነው። ይህ መሆኑ ደግሞ ሀገሪቱ ማግኘት ይገባት የነበረውን የውጭ ምንዛሪ እያሳጣት እንደሆነ ይነገራል። ችግሩን ተረድተው ቡናን እሴት ጨምረው ለተቀባይ ሀገራት የሚልኩትም በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ከነሱ ውስጥ አንዱ የሆነው ኢቲኮፍ ቴስት ትሬዲንግ የተሰኘ ተቋም ቡናን በተሻለ መንገድ እሴት ጨምሬ ወደ ውጭ ሀገራት ለመላክ ተሰናድቻለሁ ብሏል። ለመጠጣት ዝግጁ የሆኑ የቡና ምርቶችን በራሱ ፋብሪካ አሰናድቶ ያቀርባል የተባለ ሲሆን ለአንድ ሰው በሚበቃ መልኩ ተሰናድቶ መጠቀም እንዲችል ተደረጎ ተዘጋጅቷልም ተብሏል፡፡ እነዚህ ምርቶችን ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ለውጭ ማህበረሰብ፣ ኤምባሲዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ለተለያዩ አየር መንገዶች፣ ለሆቴሎች እና ለሌሎችም ተቋማት ለማውረብ ውጥን እንዳለው ተነግሮለታል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.... https://tinyurl.com/275pea5x ፋሲካ ሙሉወርቅ

የካቲት 14 2017 በምህንድስናው ዘርፍ የሰለጠኑ ወጣቶች ጀርመንኛ ቋንቋ ሰልጥነው በጀርመን ሀገር በሙያቸው የሚሰሩበት እድል መመቻቸቱ ተናገረ፡፡ ከዩኒቨርስቲ ምሩቃን ባለፈ በኮንስትራክሽን ዘርፍ በቴክኒክና ሙያ የሰለጠነም የእድሉ ተጠቃሚ ይሆናል ተብሏል፡፡ እድሉን አግኝቶ በጀርመን የስራ ላይ ስልጠና የሚጀምር ኢትዮጵያዊ መነሻ የወር ደሞዝ 1 ሺህ 80 ዩሮ ይሆናል ተብሏል፡፡ በየዓመቱ ደመወዙ እንደሚጨምር እና ተገቢው ኢንሹራንስም አንደሚገባለት ተነግሯል፡፡ የጀርመን ኮንስትራክሽን ፌዴሬሽን በኢትዮጵያ ይፋ ያደረገው አዲስ ፕሮጄክት አንዱ አላማም ይኸው መሆኑን ሰምተናል ፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ …. https://tinyurl.com/3cv6696r ትዕግስት ዘሩሁን የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q 📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd 📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s 📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il 📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r

የካቲት 14 2017 በአዲስ አበባ በያዝነው ሳምንት የእሳት ቃጠሎን ጨምሮ የተለያዩ አራት ድንገተኛ አደጋዎች አጋጥመዋል ተባለ፡፡ በ5 የአደጋ ተከላካይ ሰራተኞች ላይ ካጋጠመ መታፈን ውጭ በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋ የለም ተብሏል፡፡ ሳምንቱ እንዴት አለፈ ስንል የጠየቅነው የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን፤ በሳምንቱ በአዲስ አበባ በንብረት ላይ ጉዳት ያስከተሉ 3 የእሳት አደጋ እንዲሁም በአሳንሰር ብልሽት ምክንያት 1 አደጋ መድረሱን ነግሮናል፡፡ የተቋሙ ህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ በቦሌ አካባቢ ባለው ዋሪት ህንፃ የአሳንሰር ገመድ ተበጥሶ የ7 ዓመት ህፃንን ጨምሮ በ8 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ነግረውናል፡፡ በተጨማሪም በሳምንቱ በኮልፌ፣ በመካኒሳና በሸገር ከተማ አጃምባ አካባቢ 3 የእሳት አደጋዎች ተከስተዋል፡፡ በአደጋዎቹ እሳቱን ለማጥፋት ሰዓታትን ከፈጁ ጥረቶች በኋላ እሳቱን ማጥፋት ቢቻልም በተለይ በኮልፌ አካባቢ የደረሰው አደጋ ከበድ ያለ ነው ያሉን አቶ ንጋቱ፣ ከባድ የንብረት ጉዳት ደርሷል፤ በ5 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ላይ የመታፈን ጉዳት እንደደረሰና በሌሎች ሰዎች ላይ የደረሰ ጉዳት አንደሌለም ጠቁመዋል፡፡ በከተማዋ ያሉ የህንፃ ባለቤቶችና አገልግሎት ሰጪዎች የህንጻዎቻቸው አሳንሰሮች ደህንነት የማረጋገጥ ሃላፊነት እንዳለባቸው አንስተዋል፡፡ የአደጋዎቹ መንስኤና በንብረት ላይ የደረሰው የጉዳት መጠን እተጣራ መሆኑን የተቀሱት አቶ ንጋቱ፤ያለንበት ነፋሻማ የአየር ንብረት ለእሳት አደጋ መከሰት ምቹ ስለሆነ ጥንቃቄ አይለየን ብለዋል፡፡ አርሶ አደሮች ቆሻሻን በማቃጠል ለማስወገድ ሲሞክሩ በማሳዎች እና በደን በተሸፈኑ ከፍታ ቦታዎች የሰደድ እሳት ሊከሰት ስለሚችል ጥንቃቄ ይደረግ ተብላችኋል፡፡ ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ …. https://tinyurl.com/wcyd49ht ምንታምር ፀጋው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 📌 Website: https://shorturl.at/yCz7q 📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd 📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s 📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il 📌 Linkedin : https://tinyurl.com/yhycs5r

የካቲት 15 2017 ከ15 ዓመታት በላይ ንግግር ሲደረግበት የቆየው የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ አለም አቀፍ ህግ ሆኖ እንዲፀድቅ የሚያስችለውን ድምፅ በዚህ ዓመት በመስከረም ወር ከደቡብ ሱዳን ማግኘቱ ይታወሳል፡፡ ይህም በሁለት ወር ውስጥ የናይል ተፋሰስ የትብብር ኮሚሽን እንዲቋቋም ይፈቅዳል፡፡ ስድስት ወር ሆኖትም ኮሚሽኑ እውን አልሆነም፡፡ አዲስ አበባ ላይ የተገናኙት የናይል ተፋሰስ ሀገራት ጉባኤ ላይ የተገኘችው ግብፅ ዛሬም በተቃውሞ አቋሟ ገፍታበታለች፡፡ ኢትዮጵያ ግብፅን እረፊ ስትላት ተሰምቷል፡፡ https://youtu.be/qoTX_yj9Rqw የኔነህ ሲሳይ

#የቅዳሜ_ጨዋታ የነገ የካቲት 15 2017 የቅዳሜ ጨዋታ መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ ከቀኑ 7 ሰዓት ሲሆን የቅዳሜ ጨዋታችን፤ በሟሟሻ ይጀመራል፡፡ ሟሟሻን ተከተሎ በእሸቴ አሰፋ የሚሰናዳው የመቆያ ዝግጅት ይቀርባል፡፡ ተፈሪ አለሙ በ ትዘታ ዘ አራዳ ዝግጅቱ፤ የመጀመሪያዎቹ የገነት ጦር ትምህርት ቤት ምልምሎች ስለ ነበሩት በኋላም ጥቁር አንበሳ የሚል ስያሜ ይዘው የፋሽት ኢጣሊያን ጦርን በመፋለም ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረጉ ወጣቶች ፣ከዛሬ 90 ዓመት በፊት ለጦር ስልጠና ከየቤታቸው የወጡበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ሶስተኛውን ክፍል ይነግረናል፡፡ በቅዳሜ ጨዋታ በእንግዳ ሰዓታችን፤ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የመጀመሪያው ጉባኤ በተካሄደበትና የድርጅቱ ቻርተር በተፈረመበት ወቅት የነበረውን ሁኔታ፣ በወቅቱ የነበሩ 4 የሀገራችን ከፍተኛ የመንግስት ተወካዮችና ባለሞያዎች ድርጅቱ 50ኛ ዓመቱን ሲያከበር ያጫወቱንን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ታደምጣላችሁ። ድራማ እና ታይምለስ ክላሲክስ(Timeless Classics) በሰዓታቸው ይቀርባሉ፡፡ ሸገር 102.1 የእናንተው ሬድዮ!

የካቲት 14 2017 ያልሆኑትን ሆንን እያሉ ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያሻሽጡ ድርጅቶች መበርከታቸውን የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተናገረ፡፡ የሀገር ውስጥ አምራቾች የሚያመርቱት ምርት የጥራት ደረጃቸው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ አያደርጋቸውም ተብለዋል፡፡ ድርጅቱም ‘’የሚሞቱ ሰዎች የማይሞት ተቋምን መስርተው እንዲያልፉ ነው ጥረት እያደረኩ’’ ያለሁት ሲል ተናግሯል። የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት በኢትዮጵያ ያሉ አብዛኞቹ አምራቾች የሚያመርቱ የምርት የጥራት ደረጃቸው ባለማቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የማይችሉ መሆናቸውን አንስተው የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት እየሰራ ያለው የ #ጥራት ደረጃን ያሟሉ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሆኑ ተቋማትን ማስፋፋት ላይ ነው ብለዋል። ለጥራት ሽልማት ማወዳደር ብቻ ግባችን አይደለም የሚሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው ዋናው ግባችን የምናወዳድራቸውና ሽልማት የምንሰጣቸው ድርጅቶች በጥራት እና በልህቀት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ሆነው የሀገሪቱን ኢኮኖሚ እንዲያሻሽሉ ማስቻል ነው ሲሉ ይናገራሉ። አምራች ድርጅቶች ለምርት ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ጥራትን ባህል ማድረግ እንዳለባቸው የሚያነሱት አቶ ቴዎድሮስ ይህ ካልሆነ ግን ጫናው መልሶ አምራቾቹ ላይ ያርፋል በምርጥ ጥራት ችግርም ተጠቃሚ በማጣት ድርጅቶች እስከመዘጋት ድረስ ሊያደርሳቸው እንደሚችልም ጠቁመዋል። ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ …. https://tinyurl.com/3znawy7n ፍቅሩ አምባቸው የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… 📌 YouTube: https://tinyurl.com/ky57kspd 📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s 📌 Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il