
Ethiopian Embassy In Djibouti - የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጅቡቲ
633 subscribers
About Ethiopian Embassy In Djibouti - የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጅቡቲ
Official WhatsApp Channel of Ethiopian Embassy to Djibouti
Similar Channels
Swipe to see more
Posts

ለሚመለከተው ሁሉ፤ (ግንቦት 04/2017 ዓ.ም) የጅቡቲ ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ከዚህ ቀደም መደበኛ ያልሆኑ ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ መጀመሩ ይታወቃል። በዚህ ሂደት ውስጥ በዜጎቻችን ላይ የመብት ጥሰት ሲፈፀም እና በመረጃ የተደገፈ ሪፖርት ተጠናቅሮ ለሚኒስቴር መ/ቤቱ ሲቀርብ፣ ከኤምባሲያችን ጋር በመሆን ይህንን ለመፍታት እና በሚመለከተው አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ ቁርጠኛ መሆኑን ሚኒስቴር መ/ቤቱ ገልጿል። በዚህ መሠረት እስከአሁን ባለው ሂደት ዜጎቻችን የደመወዝ ክፍያ እና ሌሎች ተያያዥ የመብት ጥሰቶች ሲያጋጥማቸው ወደ ኤምባሲው በመምጣት እያቀረቡ ካሉት አቤቱታዎች መከካል አንዳንዶቹ የተሟላ መረጃ የያዙ ባለመሆናቸው ምክንያት ኤምባሲው ተገቢውን አሠራር ተከትሎ ለመፈጸም አስቸጋሪ ሆኖ አግኝቷል። በመሆኑም ከመብት ጥሰት፣ በተለይም ደግሞ ካልተከፈሉ ውዝፍ የደመወዝ ጥያቄዎች ጋር ተያይዞ ኤምባሲው የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች ከዚህ በታች የተመላከቱትን መረጃዎችን መሆኑን በመግለጽ፣ ዜጎቻችን እነዚህ መረጃዎች አሟልተው እንዲመጡ ኤምባሲው ያሳስባል፤ 1. የሠራተኛው ሙሉ ስም፣ ስልክ እና የመኖሪያ አድራሻ፣ 2. የአሰሪው/በዳይ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር፣ ያካተቱ መሆን እንደሚገባቸው ለመጠቆም እንወዳለን። Telegram: https://t.me/EthiopiaInDjibouti/2702

የአርቲስቶች ልዑክ በትምህርት ቤት ላይ ከኤምባሲው ጋር እንደሚሰራ ገለጸ፤ (ግንቦት 04/2017 ዓ.ም) በጂቡቲ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ኤምባሲ ለሀገራችን አርቲስቶች ልዑክ አቀባበል ያደረገ ሲሆን፣ የሚሲዮኑ ምክትል መሪ ክቡር ከበደ አበራ በተለያዩ ማህበራዊ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ከልዑኩ ጋር ውይይት አድርገዋል። ምክትል የሚሲዮን መሪው ለልዑኩ በእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸው አርቲስት ማለት ለማህበረሰቡ እና ለሀገሩ ድምጽ የሚሆን በመሆኑ፣ ሚሲዮኑ በጂቡቲ በሚያደርጋቸው ማህበራዊ ኃላፊነቶች ላይ በማሰተፍ ድምጽ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል። በተለይም ደግሞ በጂቡቲ የተጀመረው የኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ በሙያቸው በመሳተፍ ለትውልድ የሚሆን አሻራ እንዲያኖሩ አሳስቧል። ልዑኩ በበኩሉ በኤምባሲው ስለተደረገለት አቀባበል በማመስገን፣ በጂቡቲ የትምህርት ቤት ግንባታ በሁለቱ ህዝቦች መካከል ያለውን ባህል፣ ቋንቋ እና እሴት የሚያጠናክር እና ከምንም በላይ የነገ ትውልድ የሚቀረጽበት ተቋም በመሆኑ ሙያዊ እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተዋል። በቀጣይም በሌሎች ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መክረዋል። Telegram: https://t.me/EthiopiaInDjibouti/2704