Ahadu Radio And Television WhatsApp Channel

Ahadu Radio And Television

104 subscribers

About Ahadu Radio And Television

Ahadu Radio and Television is an Ethiopian media company that provides broadcasting services, including radio and television programming. It offers a variety of content such as news, entertainment, cultural programs, and educational shows aimed at the Ethiopian audience.

Similar Channels

Swipe to see more

Posts

Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 3:35:32 PM

*#አሐዱ_ትንታኔ* "በይፋ የተጀመረው የእስራኤል እና የኢራን ጦርነት!" *ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇* https://youtu.be/u2gdHHE0Gcs?si=w68WzoKEdTQt1zaZ

Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 3:34:59 PM

*በደብረ ብርሃን ከተማ ከ5 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች በሰብዓዊ ድጋፍ እጥረት ምክንያት ለችግር መጋለጣቸው ተገለጸ* ሰኔ 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በጸጥታ ችግር ምክንያት ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቅለው ከአራት ዓመት በላይ በአማራ ክልል በደብረብረሃን ከተማና በአጓራባች ወረዳዎች የሚኖሩ ከ5 ሺሕ በላይ ተፈናቃዮች በሰብዓዊ አቅርቦት ችግር ምክንያት ለተለያዩ ተላላፊና ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች ተጋላጭ እየሆኑ እንደሚገኙ አሐዱ ያነጋገራቸው ቅሬታ አቅራቢዎች ተናግረዋል፡፡ ምግብ፣ የንጽኅና መጠበቂያና መጠለያ በበቂ ሁኔታ ባለመድረሱ በሕይወታቸው ላይም ስጋት እንደቀነባቸው ገልጸዋል፡፡ ከ16 ከሚደርሱ በኦሮሚያ ክልል ከሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች መፈናቀላቸውን የተናገሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "ምንም አይነት ውሳኔ ሳይሰጠን ከአራት ዓመት በላይ በካምፕ ውስጥ እየኖርን ነው" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡ "በአሁኑ ወቅት የክልሉ መንግሥት ከ800 በላይ ድንኳኖችን በመስራት በአንድ ድንኳን ውስጥ አራት ቤተሰብ እንዲኖር አመቻችቶልን እየኖርን ነው" የሚሉ ተፈናቃዮች፤ "ነገር ግን ክረምቱ ከመቃረቡ ጋር በተያያዘ፤ የምንኖርበት መጠለያ ከዝናብ የሚከላከልም አይደልም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ "የፌደራሉ መንግሥትም ይሁን የክልሉ መንግሥት እንዴት እየኖርን እንዳለን ኢትዮጵያዊን መሆናችንን የዘነጉት ይመስለናል" ሲሉም ቅራታቸውን ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡ "አሁን ቢሆን የሚመለከተው አካል ዜጋ መሆናችንን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ወይ ቀደምት ንብረት ካፈራንበትና መኖሪያ ቀያችን አመቻችቶ መመለስ፤ ይህን ማድረግ ካልቻለ ደግሞ የክልሉ መንግሥት የጸጥታ ስጋት በሌለባቸው አካባቢዎች ጥናት አድርጎ በሰፈራ መልክ እንዲያሰፍረን እንጠይቃለን" ሲሉ አሳስበዋል፡፡ የተፈናቃዮቹን ቅሬታ መነሻ በማድረግ ለተጨማሪ መረጃ ለአማራ ክልል የአደጋና ስጋት አመራር ኮሚሽን ያደረግነዉ የስልክ ሙካራ ሳይሳካ ቀርቷል። ነገር ግን በጉዳዩ ላይ ምላሽ የሚሰጥ ከሆነ በዘገባ ሽፏን የምንመለስበት ይሆናል። በደረጄ መንግስቱ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/14/2025, 6:01:37 AM

*መልካም ቀን!* አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 4:57:55 PM

*በገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሲደረግ የቆየው ማሻሻያ ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ* ሰኔ 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በመላ ኢትዮጵያ በሚገኙ 75 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚካሄደው የማሻሻያ ሥራ አካል የሆነው የገፈርሳ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ማሻሻያ ሥራ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል፡፡ የገፈርሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ሲሰራ የነበረውን የማሻሻያ እና አቅም ማሳደግ ሥራ አጠናቆ ጣቢያው በእጥፍ አገልግሎት እንዲሰጥ የሚያደርገው አቅም ላይ ማድረሱን ነው ተቋሙ የገለጸው። ከአዲስ አበባ በቅርብ እርቀት ላይ የሚገኘው የገፈርሳ የኃይል ማከፋፈፈያ ጣቢያ የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ እና የታጠቅ ኢንደስትሪ መንደርን ጨምሮ ለሌሎችም እስከ ፊቼ ያሉ አካባቢዎችን የኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ እንደሆነ ተገልጿል። ነገር ግን ከዚህ በፊት ይነሱበት የነበሩ የኃይል መቆራረጦችን ለመፍታት በተሰራው ሥራ አሁን ላይ እስከ 200 ሜጋ ዋት ኃይል እንዲሸከም ተደርጎ መሻሻሉም ተመላክቷል። በ230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ በ230 ኪሎ ቮልት የሚያስተላልፍ ማከፋፈያን ጨምሮ፤ በ230 የተቀበለውን ኃይል ወደ 15 ኪሎ ቮልት ቀይሮ ለአነስተኛ የኃይል ፍጆታ ተጠቃሚዎች የሚያደርስ ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ መገንባቱን የተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ሞገስ መኮንን ለአሐዱ ተናግረዋል። ተቋሙ አጠቃላይ የአቅም ማሳደግ እና ማስፋፊያ ሥራዎችን በ75 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እየተሰራ ነው ተብሏል። በእመቤት ሲሳይ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 3:33:18 PM

*በ89 ካምፓሶቻቸው ስልጠና ሲሰጡ በነበሩ 57 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ* 👉 *ተቋማቱ በድጋሚ የእውቅና ፈቃድ መጠየቅ የሚችሉት ከ2 እና ከ4 ዓመታት በኋላ ነው ተብሏል* ሰኔ 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) 57 ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በ89 ካምፓሶቻቸው እየሰጡት የነበረው ትምህርት እና ስልጠና በፈቃድ አሰጣጥ ወቅት የተቀመጠውን ዝቅተኛ መስፈርት ባለማሟላቱ እርምጃ እንደተወሰደባቸው፤ የኢፌድሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡ በባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥር ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቢንያም ኤሮ፤ በተቋማቱ ላይ የተወሰደው እርምጃ የፈቃድ እድሳት እገዳና የትምህርት መስክ ስረዛ መሆኑን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡ የትምህርት ተቋማቱ ቅጣት የተጣለባቸው የመማር ማስተማር ሥራ ለማከናወን የሚያስችላቸውን ፈቃድ ከባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ሲወስዱ የገቡትን ውል ባለመፈጸማቸው እና የሥነ-ስርዓት ጥሰት ስለተገኘባቸው መሆኑን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። አክለውም፤ ውሳኔው ከመተላለፉ በፊት ባለፉት ዓመታት ትምህርታቸውን በተቋማቱ ተከታትለው ያጠናቀቁ 97 ሺሕ 567 ተማሪዎች የትምህርት ማስረጃ እና የምዝገባ መስፈርቶች እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎች መመርመራቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህም "በፍተሻው ወቅት ሐሰተኛ ማስረጃዎች፣ የ12ኛ ወይም የ10ኛ ክፍል ውጤታቸው ከዓመቱ የመቁረጫ ነጥብ በታች የሆነ ተማሪዎች፣ የሲኦሲ ፈተና ማስረጃ ያላቀረቡ፣ ፈቃድ በጊዜ አለማደስ እና ሌሎችም ችግሮች ተገኝተዋል" ብለዋል፡፡ ተቋማቱ ለተዘጉባቸው የትምህርት ዘርፎች በድጋሚ የእውቅና ፈቃድ መጠየቅ የሚችሉት ከ2 እና ከ4 ዓመታት በኋላ ነው ተብሏል። በ2017 የትምህርት ዘመን 92 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ124 ካምፓሶቻቸው 36 ሺሕ 729 ተማሪዎችን እያስተማሩ መሆኑን መረጃ መላካቸውም ተገልጿል። በእመቤት ሲሳይ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 4:58:50 PM

*ተፈናቃዮች ለፖለቲካ ዓላማ ማስፈጸሚያ እየተደረጉ ነው ሲሉ በትግራይ ክልል የሚገኙ ፓርቲዎች ገለጹ* ሰኔ 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የፌደራል መንግሥትም ሆነ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር "ተፈናቃዮችን ለፖለቲካ ዓላማ ማስፈጸሚያነት እየተጠቀሙ ነው" ሲሉ በክልሉ የሚቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡ "የፌደራሉ መንግሥትም ሆነ የቀድሞው የህወሓት አካል የነበረው ጊዜያዊ አስተዳደር ተፈናቃዮችን ወደ ቀያቸው በመመለስ ፈንታ፤ ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀሚያነት እያደረጓቸው ነው" ሲሉ የሳልሳ ወያኔ ሓርነት ትግራይና ባይቶና አባይ ትግራይ ፓርቲዎች አስታውቀዋል፡፡ "የትግራይን ሕዝብ ጥያቄ በፕሬቶሪያው ስምምነት ማነቆ ውስጥ በማስገባት የፌደራሉ መንግሥትም ሆነ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ለራሳቸው የፖለቲካ ፍላጎት ማስፈጸሚ ለመጠቀም እንጂ፤ የትግራይ ሕዝብን ከወንድምና እህት ጎረቤት ሕዝብ ጋር በጋራ አብሮ እንዲኖር ተገቢውን ሥራ እየሰሩ አይደለም" ሲሉ ለአሐዱ የተናገሩት የሳልሳይ ወያኔ ሃርነት ትግራይ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ብርሃኔ አጽብዓ ናቸው ፡፡ “የፕሪቶሪያ ስምምነት የመሬት ማካለል አይደልም" ሲሉ የተናገሩት አቶ ብርሃኔ፤ "ነገር ግን ከጦርነቱ በፊት ወደነበረበት እንመለስ የሚል ነበር" ሲሉ አስታውሰዋል፡፡ ሆኖም አሁን ባለው የትግራይ ክልል የፖለቲካ ውጥረት፤ ይህንን ማስፈጸም የሚቻልበት ዕድል በእጅጉ እየደበዘዘ በመሆኑ ስጋት ውስጥ የሚከት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ "የትግራይ ሕዝብ ከአማራ፣ ከአፋርና ከኤርትራ ሕዝብ ጋር በድንበር ተጋርቶ ለረጅም ዓመታት አብሮ የኖረ ሕዝብ ነው" ሲሉ የተናገሩት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው፤ "በተለየ መልኩ ከአማራ ክልል ጋር የተፈጠረው ፖለቲካዊ ውዝግ በሕዝብ ድምጽ ቢፈታ የተሻለ መፍትሄ ሊያመጣ ይችላል" ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡ የባይቶና አባይ ትግራይ ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በርኸ በበኩላቸው ከላይ የተነሳውን ሀሳብ የሚጋሩት ሲሆን፤ "የቀድሞው ህወሓት ሥሙን ቀይሮ አሁን የጊዜው አስተዳደር የተባለውም ሆነ የፌደራሉ መንግሥት የሕዝብ መሞትን፣ መፈነቀልና የትኛውንም የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለመከላከል እየሄዱበት ያለው እርቀት እዚህ ግባ የሚባል አይደለም" ብለዋል፡፡ ፓርቲዎቹ "አሁንም ቢሆን የትግራይ ችግር የኢትዮጵያ ችግር በመሆኑ፤ የክልሉ አመራሮችም ይሁን የፌደራል መንግሥቱ በትኩረት ሊሰሩ ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል፡፡ በፍርቱና ወልደአብ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/14/2025, 5:05:01 PM

*በክልሉ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ መቆየት ካለባቸው ጊዜ በላይ ለረዥም ዓመታት የቆዩ 115 ሕጻናት እንደሚገኙ ተገለጸ* ሰኔ 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሕጻናት በማረሚያ ቤቶች ውስጥ መቆየት የሚችሉት እስከ 1 ዓመት ከ6 ወር ብቻ ቢሆንም ለረዥም ዓመታት የቆዩ 115 ሕጻናት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ቤቶች ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ በክልል በሚገኙ 8 ማረሚያ ቤቶች ውስጥ 59 ወንድ እና 56 ሴት በድምሩ 115 ሕጻናት ከወላጆቻቸው ጋር በማረሚያ ቤት እንደሚገኙ፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ማረሚያ ቤት ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለማየሁ ማሞ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ሕጻናት በማረሚያ ቤቶች ውስጥ በተቻለ መጠን በእንክብካቤ እንዲያድጉ እና ከውጭው ማህበረሰብ ጋር በትምህርት ቤቶች እንዲገናኙ እየተደረገ ቢሆንም፤ አሁንም ሙሉ ነው ማለት እንደማይቻል እንደማይቻል ኮሚሽነር አለማየሁ አስረድተዋል፡፡ ኮሚሽነሩ "ሕጻናቱ ማረሚያ ቤት ውስጥ ከወላጆቻቸው ጋር ለሚቆዩበት የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የለም" ያሉ ሲሆን፤ "ሆኖም እድሜያቸው ከፍ ሲል ለአሳዳጊዎች እና ለተቋማት ለመስጠት ወላጆች ፈቃደኛ አይደሉም" ብለዋል፡፡ "ይህም ሕጻናቱ ለረጅም ጊዜ ማረሚያ ቤት ውስጥ እንዲቆዩ እያደረገ ነው" ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩ ይህንን ቢሉም የማረሚያ ቤቶች ማቋቋሚያ አዋጅ አንቀፅ 28 ሕጻናት ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቆየት የሚችሉት ለአንድ ዓመት ከ6 ወር ብቻ እንደሆነ ይደነግጋል፡፡ ሆኖም "በክልሉ በሚገኙት ማረሚያ ቤቶች እዚያው ተወልደውና በተለያየ የእድሜ ክልል ገብተው እየኖሩ የሚገኙ እስከ 14 ዓመት ድረስ የሆናቸው 115 ሕጻናት ይገኛሉ" ብለዋል፡፡ ይህን መሰሉ ጉዳይ በሌሎች ክልሎች በሚገኙ ማረሚያ ቤቶችም የሚስተዋል ሲሆን፤ "ሕጻናቱ በማረሚያ ቤት ለረዥም ጊዜ ሲቆዩ የሚደርስባቸውን ጫና ለመቀነስ እና የሥነ ልቦና ጉዳት እንዳያጋጥማቸው ለማድረግ ሕጉ ምን ይላል?" ሲል አሐዱ የሕግ ባለሙያ እና የኢትዮጵያ ሰራተኞች መብቶች ተሟጋች የተሰኘው ሀገር በቀል ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ ካሌድ ጌትየን ጠይቋል፡፡ በ2020 በወጣ መረጃ መሠረት በኢትዮጵያ በክልልም በከተማም ያሉት ሁሉም ማረሚያ ቤቶች ከደረጃ በታች መሆናቸውን አፍሪካን ቻይልድ ፖሊሲ በጥናቱ አሳይቷል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ "ለሕጻናት ታስበው የሚገነቡ ማረሚያ ቤቶች ባለመሆናቸው ሕጻናቱ ችግር ላይ እንደሆኑ የሚያሳይ ነው" ብለዋል፡፡ "ሕጻናት ማረሚያ ቤት መቆየት ያለባቸው ከ2 ዓመት በታች ያሉት ቢሆኑም፤ ከዚያ እድሜ በላይ ያሉትም ማረሚያ ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ" ነው ያሉት፡፡ ከበጀት አንጻርም ለሕጻናት ተብሎ ለብቻው የሚያዝ በጀት ባለመኖሩ፤ ሕጻናቱን ለምግብ እጥረት እንዲጋለጡ ሊያደርግ ይችላልም ተብሏል፡፡ በእመቤት ሲሳይ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/14/2025, 5:03:49 PM

*ለካንሰር መድኃኒት አቅራቢዎች ተደጋጋሚ ጨረታ ቢወጣም የተሳታፊዎች ብዛት ግን አነስተኛ መሆኑ ተገለጸ* ሰኔ 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሕጉን መሠረት ያደረገ ጨረታ ለካንሰር መድኃኒ አቅራቢዎች በተደጋጋሚ ጊዜ የሚወጣ ቢሆንም፤ ሥራው አዋጭ ባለመሆኑ ምክንያት የመድኃኒት አቅራቢዎቹ በጨረታው ተሳታፊ እንደማይሆኑ የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት አስታውቋል። በኢትዮጵያ ለካንሰር በሽታ 54 አይነት መድኃኒቶች እንደሚቀርቡ ለአሐዱ የገለጹት የአገልግሎቱ ዋና ዴይሬክተር አብዱልቃድር ገልገሎ (ዶ/ር)፤ "ከእነዚህም ውስጥ በኢትዮጵያ በተጠናው ጥናት መሠረት አንዳንድ መድኃኒቶች በጣም ውስን ሕመምተኛ ብቻ ያላቸው ናቸው" ብለዋል። በዚህም ምክንያት ሕመምተኞች ለመድኃኒት እጦት እንደሚጋለጡ በመግለጽም፤ ሕመምተኞች እና ምርቱ አነስተኛ ሲሆን ለሥራቸው አዋጭ ባለመሆኑ አገልግሎቱ መድኃኒቶችን የሚረከብ አቅራቢዎችን ለማግኘት እንደሚቸገር አስታውቀዋል። ዳይሬክተሩ አክለውም፤ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ መድኃኒቶችን ከሌሎች ሀገራት ለማስመጣት የሚያስችል መነሻ ሕግ ባለመኖሩ በፍላጎቱ ልክ መድኃኒት ለማስገባት አዳጋች እንደነበረ አንስተዋል። የካንሰር መድኃኒትን በተመለከተ በጤና ተቋማት በኩልም ፍላጎቱ መኖሩን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ነገር ግን ፍላጎቱ ኑሮ በሕጋዊ መንገድ የማይመጣ ከሆነ መድኃኒቱ ለኮንትሮባንድ ወይም ለሕገ-ወጥነት ተጋላጭ መሆኑ እንደማይቀር ተናግረዋል። በመሆኑም እንደ ሀገር አነስተኛ ሕመምተኛ ቢኖር እና አቅራቢ ባይገኝም እንኳ፤ ለየትኛውም ሕመምተኛ መድኃኒት የማቅረብ ግዴታ ሊኖር እንደሚገባ አንስተዋል። በዚህም መሠረት ባሳለፍነው ሳምንት ሥራ ላይ በዋለው የመድኃኒትና የሕክምና መሳሪያዎች የግዥ አፈፃፀም መመሪያ መሠረት፤ ከሌሎች ሀገራት ጋር ተመሳሳይ መድኃኒቶችን በጋራ ለመግዛትና ለመጠቀም የሚያስችል የጋራ ጥምር ግዢ አሰራር ሕግ መውጣቱን አስታውቀዋል። መመሪያው የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለቱን መሠረታዊ ችግሮች የሚቀረፍ እና ለሀገር ውስጥ አምራቾች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጥ መሆኑንም አስረድተዋል። ስለዚህም በሕጋዊ መንገድ የተመዘገበ አምራች፣ ደህንነቱ የተረጋገጠ ከሆነና ለበሽታው ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ተለይተው መንግሥት የሚፈለገውን ያህል መድኃኒት ማምጣት ከቻለ፤ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚገቡትን የካንሰር እና መሰል መድኃኒቶች በማስቀረት እጥረቱን መቅረፍ እንደሚቻል ተናግረዋል። የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በማዕከል የሚፈፀሙ የመድኃኒት አቅርቦት እና የሕክምና መሳሪያዎች የግዥ አፈፃፀም መመሪያ በቅርቡ ማጽደቁ የሚታወስ ሲሆን፤ በግዥ መመሪያው ላይም በዓለም አቀፍ ግልፅ ጨረታ ግዥ መፈፀም የሚቻልበት የገንዘብ ጣሪያ 3 ቢሊዮን ብር እንዲሆን፣ እንዲሁም የዉስን ጨረታ የገንዘብ ጣሪያ 2 ቢሊየን ብር እንዲሆን መደረጉ ተገልጿል። በስፍራሽ ደመላሽ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 3:33:53 PM

*ከውጭ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባው ምርት የጥራት ማረጋገጫ ዲጂታል አለመሆኑ ክፍተቶችን እየፈጠረ ነው ተባለ* ሰኔ 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከውጪ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ምርቶች የጥራት ማረጋገጫ የሚሰጥበት አግባብ ማኑዋል ወይም በወረቀት መሆኑ፤ በኢትዮጵያ የገቢ ምርት ዝውውር ላይ ክፍተቶችን እየፈጠረ ነው ሲል ትሬድ ማርክ አፍሪካ ለአሐዱ አስታውቋል። በኢትዮጵያ የትሬድ ማርክ አፍሪካ ዳይሬክተር እውነቱ ታየ፤ ማንኛውም የገቢ እና ወጪ ንግድ ጥራቱ ሳይረጋገጥ ወደ የትኛውም ሀገር እንደማይላክና እንደማይገባ ተናግረዋል። ነገር ግን እስካሁንም ድረስ የጥራት ደረጃው የሚያረጋገጥበት አግባብ በወረቀት ብቻ በመሆኑ እና ወረቀቶች እንደልብ በማይገኙበት ጊዜ ሥራውን በማጓተት የገቢ ምርቱ ላይ ችግር እንዳሳደረበት አንስተዋል። አክለውም በዓለም ላይ የገቢና ወጪ ንግድ ከሚፈፀምባቸው ከ100 በላይ ሀገራት መካከል የዲጂታል ስርዓቱን ባለመከተል ወደኋላ የቀረችው ኢትዮጵያ እንደሆነች ገልጸዋል። በዚህም መሠረት ትሬድ ማርክ አፍሪካ የኢትዮጵያን ገቢ እና ወጪ ንግድ ለማጠናከር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ይህንን የምርቶችን የጥራት ደረጃም በዲጂታል ስርዓት እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችሉ ሰፊ ሥራዎች መኖራቸውን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ በቅርቡም ከኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ጋር በመሆን ይፋ የሚደረግ የዲጂታል አሰራር መኖሩን አስታውቀዋል። በስፍራሽ ደመላሽ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Ahadu Radio And Television
Ahadu Radio And Television
6/13/2025, 3:29:43 PM

*ሃይንከን ኢትዮጵያ ከአዲስ ሜትር ታክሲ ጋር በመተባበር "በልክ" የተሰኘ መርሃ ግብር አስጀመረ* ሰኔ 6/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሃይንከን ኢትዮጵያ አዲስ ሜትር ታክሲን የትግበራ አጋር በማድረግ፤ አሽከርካሪዎች ከጠጡ በጭራሽ እንዳይነዱ ግንዛቤን የሚያስጨበጥ "በልክ፣ በአግባብ በኃላፊነት - አራዳ ከጠጣ የማይነዳ" የሚል ዘመቻውን ትናንት ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ አስጀምሯል፡፡ ድርጅቱ በመስቀል ፍላዎር አደባባይ ያስጀመረው ይህ መርሃ ግብር በ50 የአዲስ ሜትር ታክሲዎች ላይ መልዕክቱን በመለጠፍ ሲሆን፤ መልዕክቱ ምንም አይነት መጠጥን የሚያበረታታም ይሁን ማን መልዕክቱን እንዳስተላለፈው የሚገልጽ ምልክት የለውም። "ጠጥቶ ማሽከርከር የሚያስከትለውን አደጋ በመገንዘብ እንደ አንድ ኃላፊነት እንደሚሰማው ድርጅት ያስጀመርነው ይህ ዘመቻ በ50 ታክሲዎች ላይ መልዕክቱን በመለጠፍ ለ6 ወራት እንዲቆይ እናደርጋለን" ሲሉ የሃይንከን ኢትዮጵያ የሴስቴይነብሊቲ የውጭና መንግሥታዊ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ፍቃዱ በሻህ ተናግረዋል። ይህ መልዕክት ታክሲዎቹ ተዘዋውረው በሚሰሩበት በአዲስ አበባና በዙሪያዋ ባሉ ከተሞች በቀን ከ2 ሚልዮን በላይ ሕዝብ ይመለከተዋል ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልጸዋል፡፡ ሃይንከን ኢትዮጵያ ከዚህም ጎን ለጎን አልኮል መጠጥን በኃላፊነት መጠቀም በሚለው ዘመቻው ሥር፤ እድሜያቸው ከ21 ዓመት በታች ያሉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች (No for Underage Drinking) "አልኮል አልቀምስም" የሚል ስልጠናም እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡ የሃይንከን ምንም አሻራ ሳይገኝ ስልጠናውን የሚሰጡለት መንግሥታዊ ያልሆኑ የትግበራ አጋሮቹ ሲሆኑ፤ መርሃ-ግብሩ እስከ አሁን በመላው አገሪቱ ባሉ 11 ዩኒቨርሲቲዎች መካሄዱ ተመላክቷል፡፡ የ "በልክ" መርሀ-ግብር የሃይንከን ኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆኑት ባርት ዲ ኬኒንክ፣ የሴስቴይነብሊቲ የውጭና መንግስታዊ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ፍቃዱ በሻህ፣ የአዲስ ሜትር ታክሲ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ ኃይሉ እና የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ተወካይ አቶ ኢሳ አሰፋ እንዲሁም የትራፊክ ፖሊስ ተወካዮች በጋራ በመሆን አስጀምረውታል፡፡ #አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ *ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!* ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/ ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

Post image
Image
Link copied to clipboard!